Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/orthodox1/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tg-me/post.php on line 50
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 | Telegram Webview: orthodox1/13243 -
Telegram Group & Telegram Channel
⇨ ቀኝን እብራይስጡም ( יָמִין yaw-meen ) የውሚን የሚለው ግእዛችን የማን ያለውን ነው፤ በትርጉም the right hand or side (the south) ቀኝ እጅና አቅጣጫ ሆኖ ደቡብን ጠቋሚ ነው!
↳ ቴማን የሚለው የኤሳው የልጅ ልጅ ወይም የኤልፋዝ ልጅ መጠሪያና የቦታ ስም ትርጉሙ #ቴማን እንተየማን ወይም ደቡብ በሚል ተተርጉሟል

⇨ ግራን ዳግመኛም በሂብሩ ( שְׂמֹאול⇝ sem-ole') ሴምኦሌ የሚለው ግእዙ ፀጋም የሚለውን ሲሆን በፍቺው ; the left hand or side (the north) ሰሜን የሚለውን ዐቢይ ማእዘን የሚገልጥ ግራ እጅና የግራ አቅጣጫ ነው፤ በዚህም ለአቅጣጫው የግራ ሀካይነትና ድኩምነት መገለጫው ሆኖ የጽኑ ጥፋትና የክፉ ነገር መነሻ መሆኑ ተነግሯል፤
↳ "ወንሥኡ ጽዮነ ወአምስጡ ውስተ ጽዮን እስመ አመጽእ እኪተ ‘እምሰሜን’ … ከሰሜን ክፉ ነገርንና ጽኑ ጥፋትን አመጣለሁና ጽዮንን ያዙ ወደ ጽዮን ሽሹ" (ኤር ፬፥፮) ይላል…


ስለዚህ እኛም ፦ ወደ «ጽዮን» በመሸሽ ከጠቢቡ ሰሎሞን ጋር ሁነን ⇨ ሰሜን ሆይ ተነሥ፣ ደቡብ ሆይ ና እንበለው "ተንሥእ ሰሜን ወነዐ ደቡብ" ( መኃ ፬፥፲፮)

② #ጌባል እና #ገሪዛን (ጌባል ፀጋማይ ተራራ፣ ገሪዛን የማናይ ተራራ)
. ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈

ኹለቱም ተራሮች የዮሴፍ ልጅ የኤፍሬም ነገድ ርስት ውስጥ ይገኛሉ፤
⇨ ጌባል ፦ በስተሰሜን ያለ የተራራ ስም ሲሆን የገሪዛን አንፃር የርግማን ቃሎች የሚነገሩበት ፀጋማይ ተራራ ነው ( ዘዳ ፳፯፥ ፲፫)፡፡
⇨ ገሪዛን፦ በስተደቡብ ያለ ቍርጥ የኾኑ የቡራኬ ቃሎች የሚነገሩበት በጌባል አንጻር ያለ ተራራ ነው (ዘዳ ፳፯፥ ፲፪)፡፡

ስለዚህ እኛም ፦ "አምላክህም እግዚአብሔር ትወርሳት ዘንድ አንተን ወደምትሄድባት ምድር ባገባህ ጊዜ፥ በረከቱን በገሪዛን ተራራ መርገሙንም በጌባል ተራራ ታኖራለህ።" (ዘዳ፲፩ ፥፳፱) እንደሚል ከግራው ናባል ርቀን በበረከቱ ተራራ በገሪዛን ያለውን በቍዔተ ነፍስ ደጅ እንጠናለን።

③ #ዳክርስ እና #ጥጦስ (Dumachus and Titus)
. ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈

ከመድኃኔዓለም ቀኝና ግራ የተሰቀሉ ወንበዴዎች መጠሪያ ስም ነው፤ ፈያታዊ ዘፀጋምና ፈያታዊ ዘየማን ይላቸዋል (Dumachus on left hand and Titus on right hand) የመጠሪያ ስማቸው (ስመ ተጸውኦ) ስያሜ በእኛ ሀገር ተአምረ ኢየሱስን ጨምሮ በሌሎች ቀደምት አዋልድ መጻሕፍት የተመለከተ ሲሆን በሌሎቹም ሀገራት ቀደምት መጻሕፍትም ጭምር በተመሳሳይ አገባብ ተገልጧል፤ ለምሳሌ በሶርያ የቀደመ መዝገብ (በልሳነ ሱርስት) ጌታችን በልጅነቱ የፈፀማቸው ገቢረ ተአምራት በተዘገበበት ወንጌል "The Syriac Infancy Gospel" ወይም "Arabic Infancy Gospel" ላይ ጌታችን ገና በልጅነቱ ከእናቱ ጋር ወደግብፅ ሲሰደድ ሁለቱን ሽፍቶች እንዳገኘ እና ትንቢት እንደተናገረላቸውም ጭምር የሚዘግብ ታሪክናና በየስማቸው የሚጠቅስ አመልካች ሀተታ ይገኛል።

⇨ ዳክርስ (Dumachus) ፈያታዊ ዘፀጋምና በግራ የተሰቀለው ያልተጸጸተው ወንበዴ( Impenitent thief) ነው!
⇨ ጥጦስ (Titus) ፈያታዊ ዘየማን በቀኝ የተሰቀለው የተጸጸተው ወንበዴ (Penitent thief) ነው!

ከአበው ይኽን ገላጭ እንዲህ የምትል ረቂቅ ቅኔ እናገኛለን
. "የማናይ ርጎ ፀጋማይ ጐመን
. ወማእከሎሙ ኢየሱስ ዝግን "

ስለዚህ እኛም፦ መናዝዝ ወደሆነ የሚገባ ጸጸት ተሻግረን እንደ ጥጦስ በቀኙ ውለን "በመንግሥትህ አስበኝ" በማለት የቀኙ ጥላ እንዲያርፍብን እንትጋ።

④ #ፍየል እና #በግ (ጠሊ ወበግዕ)
. ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈

ስለ ትንሳኤ ዘጉባኤ በተነገረው የቅዱስ መጽሐፋችን ክፍል «የሰው ልጅ» ክርስቶስ በክብሩ በሚገለጥበት ጊዜ በአውደ ፍትሕ
"በጎችን በቀኙ ፍየሎችንም በግራው ያቆማቸዋል።" ይላል (ማቴ ፳፭፥፴፫) መጽሐፈ ግንዘትም " ምቅዋመ አጣሊ ርጉማን ወምቅዋመ አባግዕ ብሩካን፡፡" ብሎ ይፈታልናል።

⇨ ፍየል (ጠሊ) በምሥጢር ሽቅብ አንጋጠው ስለሚሔዱ በላታቸው ነውራቸውን ስለማይሸፍኑ ኀፍረታቸው ስለተገለጠ… ትዕቢትን በሚያበዙ ነውራቸውን በንስሐ በማይሸፍኑ ባለ "ጠዋይ ፍኖት" ( ጠማማ መንገድ) ፣ "ገብር ፀዋግ" (ክፉ ባርያ) ምሳሌ ነው!
ጠሊ ለሚለው አብዢ አጣሊ በማለት ፈንታ « አ» ን ትቶ በ“ን”ና በ“የ” ሲበዛ ግን #ጣልያን (አጣሊ ኢጣሊ አጣልያን ‘ጣልያን) ይላል ይኽንንም ብዙ ሊቃውንት ሀገር ወራሪውን ለመዝለፍ በቅኔ ሲራቀቁበት ታይቷል።

⇨ በግ (በግዕ) በአንፃሩ አቀርቅረው የሚጓዙ በላታቸው ኀፍረታቸው የሚሰውሩ መሆናቸው በትህትና ለሚኖሩ በንስሐ ኀጢአታቸውን ለሚሰውሩ "በርትዐተ ልብ" እና "በጽድቅ ምሕዋር" ለሚሔዱ ኄራን አግብርት ምሳሌ ነው!

ስለዚህ እኛም በትህትና ራሳችንን በመግዛት ወደ ነፍሳችን ጠባቂና እረኛ እንመለስ ተቆጥቶ "ከእኔ ራቁ" ሳይሆን ከበጎቹ ጋር በቀኙ የሚያውለውን "ወደ እኔ ኑ" የሚለውን ወደመስማት የሚያደርሰውን ጥበብ በማስተዋል ገንዘብ እናድርግ፤ በአስተዋይ ዘንድ ጥበብ በቀኝ እጅ ያለ በጥንቃቄና በቅንነት የተያዘን አምባር ትመስላለችና "ከመ ድጕልማ ውስተ እደ የማን ከማሁ ጥበብ በኀበ ለባዊ " እንዲል ( ሲራ ፳፩፥፳፩)

ቀኝ ያውላችሁ!

(ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ለጾመ ነነዌ ፳፻፲፩ ዓ.ም. በመንገድ የተጻፈ )



tg-me.com/orthodox1/13243
Create:
Last Update:

⇨ ቀኝን እብራይስጡም ( יָמִין yaw-meen ) የውሚን የሚለው ግእዛችን የማን ያለውን ነው፤ በትርጉም the right hand or side (the south) ቀኝ እጅና አቅጣጫ ሆኖ ደቡብን ጠቋሚ ነው!
↳ ቴማን የሚለው የኤሳው የልጅ ልጅ ወይም የኤልፋዝ ልጅ መጠሪያና የቦታ ስም ትርጉሙ #ቴማን እንተየማን ወይም ደቡብ በሚል ተተርጉሟል

⇨ ግራን ዳግመኛም በሂብሩ ( שְׂמֹאול⇝ sem-ole') ሴምኦሌ የሚለው ግእዙ ፀጋም የሚለውን ሲሆን በፍቺው ; the left hand or side (the north) ሰሜን የሚለውን ዐቢይ ማእዘን የሚገልጥ ግራ እጅና የግራ አቅጣጫ ነው፤ በዚህም ለአቅጣጫው የግራ ሀካይነትና ድኩምነት መገለጫው ሆኖ የጽኑ ጥፋትና የክፉ ነገር መነሻ መሆኑ ተነግሯል፤
↳ "ወንሥኡ ጽዮነ ወአምስጡ ውስተ ጽዮን እስመ አመጽእ እኪተ ‘እምሰሜን’ … ከሰሜን ክፉ ነገርንና ጽኑ ጥፋትን አመጣለሁና ጽዮንን ያዙ ወደ ጽዮን ሽሹ" (ኤር ፬፥፮) ይላል…


ስለዚህ እኛም ፦ ወደ «ጽዮን» በመሸሽ ከጠቢቡ ሰሎሞን ጋር ሁነን ⇨ ሰሜን ሆይ ተነሥ፣ ደቡብ ሆይ ና እንበለው "ተንሥእ ሰሜን ወነዐ ደቡብ" ( መኃ ፬፥፲፮)

② #ጌባል እና #ገሪዛን (ጌባል ፀጋማይ ተራራ፣ ገሪዛን የማናይ ተራራ)
. ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈

ኹለቱም ተራሮች የዮሴፍ ልጅ የኤፍሬም ነገድ ርስት ውስጥ ይገኛሉ፤
⇨ ጌባል ፦ በስተሰሜን ያለ የተራራ ስም ሲሆን የገሪዛን አንፃር የርግማን ቃሎች የሚነገሩበት ፀጋማይ ተራራ ነው ( ዘዳ ፳፯፥ ፲፫)፡፡
⇨ ገሪዛን፦ በስተደቡብ ያለ ቍርጥ የኾኑ የቡራኬ ቃሎች የሚነገሩበት በጌባል አንጻር ያለ ተራራ ነው (ዘዳ ፳፯፥ ፲፪)፡፡

ስለዚህ እኛም ፦ "አምላክህም እግዚአብሔር ትወርሳት ዘንድ አንተን ወደምትሄድባት ምድር ባገባህ ጊዜ፥ በረከቱን በገሪዛን ተራራ መርገሙንም በጌባል ተራራ ታኖራለህ።" (ዘዳ፲፩ ፥፳፱) እንደሚል ከግራው ናባል ርቀን በበረከቱ ተራራ በገሪዛን ያለውን በቍዔተ ነፍስ ደጅ እንጠናለን።

③ #ዳክርስ እና #ጥጦስ (Dumachus and Titus)
. ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈

ከመድኃኔዓለም ቀኝና ግራ የተሰቀሉ ወንበዴዎች መጠሪያ ስም ነው፤ ፈያታዊ ዘፀጋምና ፈያታዊ ዘየማን ይላቸዋል (Dumachus on left hand and Titus on right hand) የመጠሪያ ስማቸው (ስመ ተጸውኦ) ስያሜ በእኛ ሀገር ተአምረ ኢየሱስን ጨምሮ በሌሎች ቀደምት አዋልድ መጻሕፍት የተመለከተ ሲሆን በሌሎቹም ሀገራት ቀደምት መጻሕፍትም ጭምር በተመሳሳይ አገባብ ተገልጧል፤ ለምሳሌ በሶርያ የቀደመ መዝገብ (በልሳነ ሱርስት) ጌታችን በልጅነቱ የፈፀማቸው ገቢረ ተአምራት በተዘገበበት ወንጌል "The Syriac Infancy Gospel" ወይም "Arabic Infancy Gospel" ላይ ጌታችን ገና በልጅነቱ ከእናቱ ጋር ወደግብፅ ሲሰደድ ሁለቱን ሽፍቶች እንዳገኘ እና ትንቢት እንደተናገረላቸውም ጭምር የሚዘግብ ታሪክናና በየስማቸው የሚጠቅስ አመልካች ሀተታ ይገኛል።

⇨ ዳክርስ (Dumachus) ፈያታዊ ዘፀጋምና በግራ የተሰቀለው ያልተጸጸተው ወንበዴ( Impenitent thief) ነው!
⇨ ጥጦስ (Titus) ፈያታዊ ዘየማን በቀኝ የተሰቀለው የተጸጸተው ወንበዴ (Penitent thief) ነው!

ከአበው ይኽን ገላጭ እንዲህ የምትል ረቂቅ ቅኔ እናገኛለን
. "የማናይ ርጎ ፀጋማይ ጐመን
. ወማእከሎሙ ኢየሱስ ዝግን "

ስለዚህ እኛም፦ መናዝዝ ወደሆነ የሚገባ ጸጸት ተሻግረን እንደ ጥጦስ በቀኙ ውለን "በመንግሥትህ አስበኝ" በማለት የቀኙ ጥላ እንዲያርፍብን እንትጋ።

④ #ፍየል እና #በግ (ጠሊ ወበግዕ)
. ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈

ስለ ትንሳኤ ዘጉባኤ በተነገረው የቅዱስ መጽሐፋችን ክፍል «የሰው ልጅ» ክርስቶስ በክብሩ በሚገለጥበት ጊዜ በአውደ ፍትሕ
"በጎችን በቀኙ ፍየሎችንም በግራው ያቆማቸዋል።" ይላል (ማቴ ፳፭፥፴፫) መጽሐፈ ግንዘትም " ምቅዋመ አጣሊ ርጉማን ወምቅዋመ አባግዕ ብሩካን፡፡" ብሎ ይፈታልናል።

⇨ ፍየል (ጠሊ) በምሥጢር ሽቅብ አንጋጠው ስለሚሔዱ በላታቸው ነውራቸውን ስለማይሸፍኑ ኀፍረታቸው ስለተገለጠ… ትዕቢትን በሚያበዙ ነውራቸውን በንስሐ በማይሸፍኑ ባለ "ጠዋይ ፍኖት" ( ጠማማ መንገድ) ፣ "ገብር ፀዋግ" (ክፉ ባርያ) ምሳሌ ነው!
ጠሊ ለሚለው አብዢ አጣሊ በማለት ፈንታ « አ» ን ትቶ በ“ን”ና በ“የ” ሲበዛ ግን #ጣልያን (አጣሊ ኢጣሊ አጣልያን ‘ጣልያን) ይላል ይኽንንም ብዙ ሊቃውንት ሀገር ወራሪውን ለመዝለፍ በቅኔ ሲራቀቁበት ታይቷል።

⇨ በግ (በግዕ) በአንፃሩ አቀርቅረው የሚጓዙ በላታቸው ኀፍረታቸው የሚሰውሩ መሆናቸው በትህትና ለሚኖሩ በንስሐ ኀጢአታቸውን ለሚሰውሩ "በርትዐተ ልብ" እና "በጽድቅ ምሕዋር" ለሚሔዱ ኄራን አግብርት ምሳሌ ነው!

ስለዚህ እኛም በትህትና ራሳችንን በመግዛት ወደ ነፍሳችን ጠባቂና እረኛ እንመለስ ተቆጥቶ "ከእኔ ራቁ" ሳይሆን ከበጎቹ ጋር በቀኙ የሚያውለውን "ወደ እኔ ኑ" የሚለውን ወደመስማት የሚያደርሰውን ጥበብ በማስተዋል ገንዘብ እናድርግ፤ በአስተዋይ ዘንድ ጥበብ በቀኝ እጅ ያለ በጥንቃቄና በቅንነት የተያዘን አምባር ትመስላለችና "ከመ ድጕልማ ውስተ እደ የማን ከማሁ ጥበብ በኀበ ለባዊ " እንዲል ( ሲራ ፳፩፥፳፩)

ቀኝ ያውላችሁ!

(ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ለጾመ ነነዌ ፳፻፲፩ ዓ.ም. በመንገድ የተጻፈ )

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/13243

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Why Telegram?

Telegram has no known backdoors and, even though it is come in for criticism for using proprietary encryption methods instead of open-source ones, those have yet to be compromised. While no messaging app can guarantee a 100% impermeable defense against determined attackers, Telegram is vulnerabilities are few and either theoretical or based on spoof files fooling users into actively enabling an attack.

Telegram hopes to raise $1bn with a convertible bond private placement

The super secure UAE-based Telegram messenger service, developed by Russian-born software icon Pavel Durov, is looking to raise $1bn through a bond placement to a limited number of investors from Russia, Europe, Asia and the Middle East, the Kommersant daily reported citing unnamed sources on February 18, 2021.The issue reportedly comprises exchange bonds that could be converted into equity in the messaging service that is currently 100% owned by Durov and his brother Nikolai.Kommersant reports that the price of the conversion would be at a 10% discount to a potential IPO should it happen within five years.The minimum bond placement is said to be set at $50mn, but could be lowered to $10mn. Five-year bonds could carry an annual coupon of 7-8%.

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from no


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA